በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ተረጂነትን በማስቀረት ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል “ከልመና ወደ ብልፅግና” የመሻገርና አገራዊ ክብርን የማስጠበቅ ግብ በመሰነቅ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር “ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ቃል በሐዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የአደጋ…
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ታላሚ ያደረገ የተቀናጀ የአንጀት ትላትል መከላከያ ማህበረሰብ አቀፍ መድሀኒት እደላ ዘመቻ በይፋ ተጀመረ።
በክልላችን የሚገኙ 48 ወረዳዎችን ታላሚ ያደረገውና ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መድኃኒት የሚያገኙበት የማህበረሰብ አቀፍ የጤና ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል። የጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቢሮ ሀላፊ ተወካይ አቶ ኃይሌ ዘውዴ ዘመቻውን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ “ህብረተሰቡን ለጤናና ለማህበራዊ ጉዳት የሚዳርጉ የአንጀት ጥገኛ ትላትሎችን ለማጥፋት የሚሰጠው መድኃኒት ውጤታማ እንዲሆን የሁሉንም አካላት ቅንጅታዊ ስራ ይጠይቃል” ብለዋል።…
በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ ስልጣን የሚገኘው በምርጫ ብቻ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።
በምርጫ ወቅት የፖሊስ ሚናና ስነምግባር በሚል ርዕሰ ጉዳይ በካፋ ዞን ለሚገኙ የፖሊስ አባላት በቦንጋ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የመረጃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር በላይነህ በቀለ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተሳተፊ የሚሆኑ የጸጥታ አካላት ሚናቸውንና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መረዳትና ማወቅ ይገባቸዋል ብለዋል። ይህም ምርጫው በሠላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅና የፖሊስ አባላት ስነምግባርን…
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) መልዕክት
ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል። በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደረጉ ቁልፍ ስምምነቶች ልውውጥን በጋራ የመራን ሲሆን፤ የታዳሽ፣ የተቀናጀ እና ዘላቂ ኃይል እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ፕሮግራምን ለመተግበር የሚውል የ54.6 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት፣ እና የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የመንግሥትና የግል አጋርነት አዲስ የማዕቀፍ እና የፍኖተ ካርታ ልውውጥ ይገኙበታል።
ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት 8 ዓመታት ውስጥ የተዘነጉ እንደምዕራብ ኦሞ ዞኖች ያሉትን በመመልከት የመልማት ጥያቄዎችን በአግባቡ የመለሰ ፓርቲ ነው ፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በደቡብ ምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ከተማ በመገኘት ለ7ኛ ዙር ሀገራዊ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂደዋል። በዞኑ ጀሙ ከተማ በተካሄደው የይምረጡኝ ቅስቀሳ መድረክ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ባለፉት ዓመታት በሰጣችሁን ይሁንታ መሰረት ላከናወንነው ተግባራት ከጎናችን መሆናችሁን በይፋ ስለገለጻችሁ አመሰግናለሁ ብለዋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ የነበረውን ኋላ ቀርነትና…
በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ ብሬንትፎርድን 2 ለ 1 አሸንፏል።
በኦልድ ትራፎርድ በተደረገው ጨዋታ ካስሜሮ እና ቤንጃሚን ሼሽኮ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ማቲያስ የንሰን የብሬንትፎርድን አንድ ግብ አስገኝቷል። ከጨዋታው ሦስት ነጥብ ያገኘው ዩናይትድ በ61 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፋይዳ መታወቂያ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር ከ41 ሚሊዮን በላይ ደረሰ
በኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የወሰዱ ዜጎች ቁጥር ከ41 ሚሊዮን በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ መረጃ ያመለክታል። ተቋሙ በ2018 ዓ.ም ዲጂታል መታወቂያውን ለ70 ሚሊዮን ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ አቅዶ እየሠራ ይገኛል። በዓመቱ 160 ተቋማትን ከፋይዳ ጋር ለማስተሳሰር ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ ባለፉት 9 ወራት 132 ድርጅቶችን ከሥርዓቱ ጋር ማገናኘት ተችሏል። በሌላ በኩል፣ የዜጎችን ዲጂታል ክህሎት ለማበልጸግ እየተተገበረ ባለው…


